ባሕርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፉ።

123
ባሕር ዳር: ሚያዝያ 06/2015 ዓ.ም (አሚኮ)በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሣምንት ጨዋታ ባሕርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 1 አሸነፈ፡፡
ባሕዳር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 9፡00 ላይ በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን አካሂደዋል፡፡
በዚህም ሀብታሙ ታደሠ በመጀመሪያው አጋማሽ ባስቆጠራቸው ሁለት ግቦች እና ዱሬሳ ሹቢሳ በሁለተኛው አጋማሽ ባስመዘገባት አንድ ግብ ባሕርዳር ከተማ ማሸነፍ ችሏል፡፡
የድሬዳዋ ከተማን ብቸኛ ግብ በሁለተኛው አጋማሽ ቢንያም ጌታቸው አስቆጥሯል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleሁሉ ተፈጸመ!
Next article“ጠዋት በነጋ ጊዜ በቃ ይሠቀል ብለው ደመደሙ” የቅኔ እና የአዲስ ኪዳን መምህር ጥቀኄር ወርቄ