የአማራ ክልል ምክር ቤት ከሕግ አስፈጻሚ፣ ሕግ ተርጓሚ አካላትና ከሕዝብ ክንፍ መሪዎች ጋር እየተወያዬ ነው፡፡

241

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 28/2012 ዓ.ም (አብመድ) በውይይቱ የመንግሥትን የሕግ አስከባሪነት ብቻ ሳይሆን የሕግ አክባሪነትም ለማጠናከር የተዘጋጀ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰሙ ማሞ ተናግረዋል፡፡
ክልላዊና ሀገራዊ ሠላምን ለማረጋገጥ የሕግ የበላይነት መከበር እንዳለበት ያመላከቱት ወይዘሮ ወርቅሰሙ ውይይቱ ጥሩ ግብዓት እንደሚገኝት ያላቸውን ተስፋም ገልጸዋል፡፡
ወይይቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመሥገን ጥሩነህ እየመሩት፤ የውይይት መነሻ ጽሑፍ ደግሞ በአቶ ገረመው ገብረጻድቅ እየቀረበ ነው፡፡
ዘጋቢ፡- አብርሃም በዕውቀት

Previous articleበተከሰተው የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ እና በድርቅ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የእንስሳት መኖ እጥረት ለመቅረፍ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
Next articleየባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምስለ ሕክምና ማሰልጠኛ ማዕከል ተከፈተ።