
ባሕር ዳር: ሚያዝያ 05/2015 ዓ.ም (አሚኮ)በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ የዐቢይ ጾም ስምንተኛ ሳምንት “ሰሙነ ሕማማት” በመባል ይታወቃል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የባሕርዳር ማዕከል ሰባኬ ወንጌል መምህር ለይኩን አዳሙ ከአሚኮ ኦንላይን ጋር ቆይታ አድርገው የሰሙነ ሕማማትን ምንነት እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎችን ነግረውናል። ሳምንቱ በዐቢይ ጾም መጨረሻ ከዕሑድ ጀምሮ እስከ ትንሣዔ ያሉ ቀናትን ያጠቃልላል።
እንደ መምህር ለይኩን ገለጻ ሰሙነ ሕማማት የሚለው ቃል “ሰሞን” እና “ሕማማት” ከሚሉ ሁለት ጥምር ቃላት የተመሠረተ ስም ሲሆን “ሰሙን” የሚለው ቃል ሰሞን ወይም አንድ ሳምንት ማለት ነው። ከዕሑድ እስከ ዕሑድ፣ ስምንት ቀን የሚል ትርጉም ያለው ሐሳብ ነው። “ሕማማት” የሚለው ደግሞ “ሐመ ታመመ” ከሚለው ከግዕዝ ግሥ የተገኘ ቃል ሲኾን ትርጉሙም ሕመሞች ፣ደዌዎች ፣መከራዎች ፣ስቃዮች ማለት ነው።
ስለዚህ ሰሙነ ሕማማት የሚለው ጥምር ቃል የሕማሞች ሳምንት የሚል ትርጓሜ ይኖረዋል። ይኸውም ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ እጅ ተይዞ ተገርፎ ፣ተሰቅሎ መሞቱን በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ የሚታሰብበት ሳምንት ነው።
ከመጀመሪያው ዕሑድ እስከ ትንሳዔ ቀን ያሉ የሰሙነ ሕማማት ዕለታት የየራሳቸው ስያሜ አላቸው። መምህር ለይኩን በነገሩን መሰረት:-


በዚህ ዕለት አዳምና ሔዋን ከገነት እንደተባረሩ፣ የበለስ ቅጠል እንዳገለደሙ ይታሰባል። ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ እንደጻፈው ኢየሱስ ክርስቶስ በበዓለ ሆሳዕና በመሸ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ። በማግሥቱም ከቢታንያ ሲወጡ ተራበ። ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ምናልባት አንዳች ይገኝባት እንደ ኾነ ብሎ መጣ። የበለስ ወራት አልነበረምና ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም። በዚያን ጊዜ “ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ” ብሎ ረገማት። ስለዚህም በሰሙነ ሕማማት የሚገኘው ሰኞ “መርገመ በለስ” የተፈጸመበት ዕለት መታሰቢያ ነው። የዚህም ትርጉም ወይም ምሥጢሩ ከበለስ ፍሬ መሻቱ ከሰው ፍቅር ተርቦ ማጣቱን ለመግለጽ ነው፡፡ ፍሬ የማያፈራ ዛፍ እንደሚቆረጥና ቅጠሎቹም እንዲቃጠሉ የተነገረውን በማስታወስ ሰው ሁሉ መልካም ፍሬን ሊያፈራ እንደሚገባ ለመግለጽም ታስቦ ነው።


የካህናት አለቆችና የአይሁድ ሽማግሌዎች እንዲሁም ጸሐፍት ፈሪሳውያን ክርስቶስን ለመግደል የመጨረሻውን ምክክር ያደረጉት ከዕለተ ሆሳዕና ማግስት በሚውለው ሰኞ፣ ማክሰኞ እና ረቡዕ ነበር። ሰኞና ማክሰኞ ይሰቀል፣ አይሰቀል በሚለው ክርክር ከውሳኔ ሳይደርሱ ተበትነዋል ። በመጨረሻም በዕለተ ረቡዕ ይሰቀል፤ ይገደል በሚለው ተሰማምተውበታል ። በዚህም የተነሳ ዕለተ ረቡዕ “ምክረ አይሁድ” ይባላል።
ሌላው በዕለተ ረቡዕ የተፈጸመው ተግባር መላ ዘመኗን በዝሙት ኃጢአት ያሳለፈች ሴት ወደ ክርስቶስ መጥታ ስለኃጢአቷ ይቅርታ በኢየሱስ እግር ሥር ተደፍታ ማልቀሷ የሚታሰብበት ዕለት ነው። በዚህ እለት ይሁዳ ክርቶስን አሳልፎ ሊሰጥ በ30 ብር ተደራድሮ የተስማማበትና የተዋዋለበት ዕለትም ነው።




ፋሲካ ማለት “አለፈ” ማለት ነው። መርገም፣ ሞት፣ ባርነት፣ ጨለማ ፣ድንቁርና በአጠቃላይ ክፉ አገዛዝ የተሻረበት እና የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤው የተረጋገጠበት ልዩ የደስታ ዕለት ማለት ነው።
ለእምነቱ ተከታዮች በሙሉ መልካም የትንሳዔ በዓል ይሁንላችሁ! ለኢትዮጵያዊያን መጭው ዘመን ሁሉ የደስታ ይሁን!
ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!