“ኢፍጣራችን ለወገናችን” በሚል መሪ መልእክት ሦስተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሄደ።

89
ባሕርዳር: መጋቢት 30/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ታላቁ ኢፍጣር በኢትዮጵያ ሦስተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ-ግብር ነው በአዲስ አበባ የተካሄደው።
መርሐ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የዛሬው መርሐ-ግብር በጦርነት እና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን ድጋፍ የምናሰባስብበት በመሆኑ ደስታችንን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል ብለዋል።
ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ በበኩላቸው፣ በሀገር ደረጃ ለሦስተኛ ጊዜ የተካሄደው መርሐ-ግብሩ ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ገልጸው፣ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ አንድነቱን እና ሀገራዊ አብሮነቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚጠቅምም ተናግረዋል።
በመርሐ-ግብሩ ከተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች የተወጣጡ በሺዎች የሚቆጠሩ የእምነቱ ተከታዮች ተገኝተዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የጉባ ኮርስ እና የድህረ ምረቃ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቁ ነው።
Next article“ወጥ የኾነ ሀገራዊ የጸጥታና ደህንነት ኃይል እንዲኖር የሚያደርገውን ልዩ ኀይሉን መልሶ የማደራጀት ሥራ ተጀምሯል” የክልል የሰላምና ደኅንነት ቢሮ ኀላፊዎች