መከላከያ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ለደቡብ ዕዝ የገነባውን የጦር መምሪያ ካምፕ አስመረቀ።

142
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 23/2015 ዓ.ም (አሚኮ) መከላከያ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ለደቡብ ዕዝ የሰራውን የጦር መምሪያ የሻለቃ መኖሪያና መሥሪያ ካምፕ በዛሬው እለት አስመርቋል።
በምረቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ጀነራል መኮንኖች፣ የጋሞ የሀገር ሽማግሌዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘመናዊ ካምፑ የኮር ጠቅላይ መምሪያና የሬጅመንት ጠቅላይ ሠፈር በርካታ ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጡ ግንባታዎች ያካተተ መሆኑን የግንባታው ፕሮጀክት ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ዳኛቸው ያዴታ ለኢዜአ ገልጸዋል።
ካምፑ የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ ሆስፒታልና የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ እንዲሁም የመሰብሰቢያ፣ የመመገቢያ አዳራሾችና የመዝናኛ ማዕከላት መያዙን ገልጸዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየሆስፒታል አለመኖር ያሳደረው ተፅእኖ
Next articleኢትዮጵያ እና ጀርመን የ17 ሚሊዮን ዩሮ የደን እና የደን ውጤቶች ልማት ሥምምነት ተፈራረሙ፡፡