ወልድያ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

118
ወልድያ፡ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ዩኒቨርሲቲው በጤና ሳይንስ ኮሌጅ ካሰለጠናቸው ተማሪዎች በተጨማሪ በልዩ ልዩ የትምህርት ዘርፎች በድህረ ምረቃ 112 ሰልጣኞችን አስመርቋል።
ዩኒቨርስቲው ከቅዱስ ላሊበላ ቅርስና ጥናት ግቢ 25 ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ በድህረ ምረቃ መርሀ ግብር አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ዕለት 160 ሴት አና 430 ወንድ በድምሩ 592 ተማሪዎችን አስመርቋል።
የዩኒቨርሲቲው ኘሬዝዳንት አበበ ግርማ ( ዶ.ር) ዩኒቨርሲቲው በወልድያ፣ በመርሳና በላሊበላ ግቢዎች በጤና፣ በቱሪዝም፣ በግብርናና በቴክኖሎጂ የልህቀት ማዕከላት እየሠራ ይገኛል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከ2004 ዓ ·ም ጀምሮ የምርምርና የልህቀት ሥራ እየሠራ ይገኛል።
ዘጋቢ፦ ካሳሁን ኃይለሚካኤል
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“አረጋውያን አባቶች ሀገራቸውን ጠብቀው ሲያቆዩ የተጠቀሙበትን ጥበብ ለትውልድ ሊያስተላልፉ ይገባል” የአማራ ክልል አረጋውያን ማኅበር
Next articleየኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስናና በጤና ዘርፍ የጎረቤት ሀገር ወታደሮች የተካተቱበት የምረቃ መርሃ ግብር እያካሄደ መኾን ገለጸ።