የስዊድን የጤና እና የማኅበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር የሚመራ ልዑካን ቡድን ጤና ሚኒስቴርን ጎበኘ፡፡

113

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 24/2012 ዓ.ም (አብመድ) የስዊድን የጤና እና የማኅበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ሌና ሀሌንገር የሚመራ ልዑክ ዛሬ በጤና ሚኒስቴር በመገኘት ጉብኝት አድርጓል::

ከልዑካን ቡድኑ ጋር የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት እንዲሁም በዘርፉ በትብብር የሚሠሩ ሥራዎች ላይ ውይይት እንዳደረጉ የኢትዮጵያ የጤና ሚኒስትር አሚር አማን (ዶክተር) ተናግረዋል፡፡

ዶክተር አሚር የልዑካን ቡድኑ ላደረገው ጉብኝት በራሳቸውና በመሥሪያ ቤታቸው ስም ምሥጋና አቅርበዋል፡፡

ሁለቱ አገራት በጤና ዘርፍ በአጋርነት ብዙ ሥራዎችን እንደሚሠሩ ሙሉ እምነት እንዳላቸውም ኢ.ፕ.ድ ዘግቧል፡፡

Previous article‹‹የዩኒቨርሲቲው አሠራር እንዳንሸጋገር አድርጎናል፤ ሳንሸጋገርም ሥራውን እንድንለቅ መመሪያ መተላለፉ ተገቢ አይደለም›› ሲሉ በማኅበር ተደራጅተው የሚሠሩ ወጣቶች ተናገሩ፡፡
Next articleየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሁሉም ቋንቋ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ማሰልጠኛ ማዕከል እንዲከፈት ወሰነ፡፡