ሎሬት ዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

306
ባሕር ዳር :መጋቢት 12/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በብዝሃ ሕይወት ሳይንቲስትነት አንቱታን ያተረፉት ሎሬት ዶክተር ተወልደብርሃን ገብረእግዚአብሔር ባደረባቸው ሕመም በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የአካባቢ ጥበቃ ተቆርቋሪ እና ተከራካሪ የነበሩት ዶክተር ተወልደብርሃን ገብረእግዚአብሔር ከአባታቸው ከቄስ ገብረእግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከእናታቸው ወይዘሮ መዓዛ ወልደ መድኅን በትግራይ ክልል ዐድዋ ርባገረድ መንደር የካቲት 12 ቀን 1932 ዓ.ም ተወለዱ።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በንግሥተ ሳባ 1ኛ ደረጃ እንዲሁም ወደ ጀኔራል ዊንጌት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በማምራት በ1959 ዓ.ም በከፍተኛ ውጤት ወደ ቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል።
ሎሬት ዶክተር ተወልደብርሃን በሕይወት ዘመናቸው ለሀገራቸው ያበረከቱት አስተዋጽኦ እና አርዓያነታቸው በጉልህ ቀለም ከሚጻፍላቸው ጀግና ኢትዮጵያዊያን መካከል በግንባር ቀደምትነት የተቀመጡ ነበሩ።
በብዝሃ ሕይወት ጥናት እና ምርምርም በርካታ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን ማግኘት ችለዋል።
ዶክተር ተወልደ ብርሃን የሦስት ሴቶች ልጆች አባት ሲሆኑ ከ60 በላይ ሌሎች ልጆችን ያሳደጉ ልበ ቀና ሰው ነበሩ።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“የአካባቢን ሃብት አውቆ ማልማት ከድኅነት ለመላቀቅ ብቻ ሳይሆን ተሰሚነትንም ማረጋገጥ ነው” ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ጀንበር(ዶ.ር)
Next articleበ90 ቀናት ከ3000 በላይ የመማሪያ ክፍሎች ተገንብተው ለአገልግሎት ማስጀመር የሚያስችል የቃል ኪዳን ሰነድ ተፈረመ፡፡