የንጉስ ተክለሃይማኖት ቤተመንግሥትን የማልማት ሥራ መጀመሩን የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ገለጸ።

56
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 06/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ማርቆስ ከተማ የንጉስ ተክለሃይማኖት ቤተ መንግሥት አካል የኾነና ለረዥም ጊዜ ታጥሮ የነበረን ቦታ ለማልማት የእድሳት ሥራ መጀመሩን የከተማ አሥተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ አስታውቋል።
የመምሪያው ኀላፊ አቶ መንግሥት ጅጋር እንደገለፁት፤ ከተማ አሥተዳደሩ የንጉስ ተክለሃይማኖትን ቤተ መንግሥት በማደስ የቱሪስት መዳረሻ እንዲኾንና የአካባቢው ማኅበረሰብ እንዲጎበኘው ለማድረግ ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መንገድ ለመሥራት በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል ብለዋል።
May be an image of 1 person, standing and sky
የቤተ መንግሥቱ አንድ አካል የኾነው ከአደባባዩ በስተጀርባ ለረዥም ጊዜ ታጥሮ የነበረውን ቦታ ለማልማት ከ5ሚሊየን ብር በላይ በመመደብ በይፋ ሥራ መጀመሩን የገለፁት አቶ መንግሥት የማልማት ሥራውንም መንቆረር ኮንስትራክሽን እየሠራ ነው ብለዋል።
የሚለማው ቦታ መልካምድር አቀማመጡ አስቸጋሪ በመኾኑ በጥራት እንዲሠራ መምሪያቸው አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ አቶ መንግሥት ጅጋር መናገራቸውን የከተማ አሥተዳደሩ መንግሥት ኮሙኑኬሽን ጉዳዮች።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleኢትዮጵያ እና አሜሪካ በልማት እና የዴሞክራሲ ግንባታ ሥራዎች እና መሰል ጉዳዮች ላይ መከሩ።
Next articleበደቡብ ወሎ ዞን በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ዝናብ ጉዳት የደረሰባቸው አርሶ አደሮች ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠየቁ።