“አርሶ አደሩ ሳይበለጽግ ኢትዮጵያ በለጸገች ማለት አይቻልም!” ዶክተር ይልቃል ከፋለ በክልሉ ትላልቅ የመስኖ ልማት ግድቦችን ተደራሽነት ማስፋት በጣም አስፈላጊ ናቸው።

98
በተወሰኑ አካባቢዎች የተገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች ሥራ ተጀምረዋል።
የመስኖ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ በመግባታቸው በአማራ ክልል ለመጀመሪያ ጊዜ በበጋ ወቅት ብቻ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት ተችሏል፡፡ ለዚህ ውጤት መገኘት የመስኖ ፕሮጀክቶች ሥራ መጀመር በመቻላቸው ነው፡፡
ክልላችን የከርሰ ምድርና ገጸ-ምድር ውኃ ባለጸጋ ነው። ጸጋውን አልምቶ መጠቀም ደግሞ ያልተቋረጠ ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል። አርሶ አደሩ በስፋት ዘመናዊ የውኃ መሳቢያ ፓምፕ መጠቀም በመቻሉ በግብርና ሥራው ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ችሏል፡፡ በቀጣይም ትላልቅ ወንዞች ባሉበት የክልላችን አካባቢ የመስኖ ግድቦችን እንሠራለን፡፡
በአማራ ክልል በቂ ምርት አለ፤ ምርት እንደሌለ በማስመሰል የኢኮኖሚ አሻጥር በሚሠሩና ያለ አግባብ ምርት በሚሰበስቡ ነጋዴዎን እና ደላላዎች ላይ መንግሥት ጥብቅ ቁጥጥር ያደርጋል፡፡ ይህን ማድረግ ስንችል እየታየ ያለውን ሰው ሠራሽ የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት መመለስ እንችላለን፡፡
May be an image of grassየገበያው ጉድለት በዘላቂነት የሚሞላው ምርታማነትን በተገቢው ደረጃ ማሻሻል ስንችል ነው። የዋጋ ግሽበትንና ሰው ሠራሽ የኑሮ ውድነትን መቀነስ የምንችለው በአንድ ማሳ ላይ በዓመት ሶስት ጊዜ ማምረትን ባህል ማድረግ ስንችል።
አርሶ አደሩ ሳይበለጽግ ኢትዮጵያ በለጸገች ማለት አይቻልም፡፡ በአጠቃላይ የሀገርን ልማት ለማፋጠን
አርሶ አደሩ ላይ ትኩረት አድርገን መሥራታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡
ዶክተር ይልቃል ከፋለ
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መሥተዳድር
መረጃው የርእሰ መሥተዳድር ጽሕፈትቤት ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየ2ኛው ምዕራፍ ሀገር አቀፍ የልማታዊ ሴፍቲኔት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Next articleበክልሉ የሚሰሩ የመሰረተ ልማት አውታሮች የአካባቢና ማኅበረሰብ ደህንነትን መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ ለማስቻል እየሰራ መሆኑን የአማራ ክልል የአካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ።