
ሁመራ:መጋቢት 04/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በጉብኝቱ የአማራ ክልል ኀብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት አመራሮች ፣ የዞን ባለሙያዎች እና የጤና ተቋማት ኀላፊዎች ተሳትፈዋል።
በጉብኝታቸውም በባለፈው ሥርዓት የወልቃይት ጠገዴ አማራ ተወላጆች በማንነታቸው ብቻ በግፍ የታሰሩበትንና የተገደሉበትን ” ባዶ ስድስት” የጅምላ መቃብርን ተመልክተዋል።
በተጨማሪም በአጼ በካፋ ዘመነ መንግሥት በደጅ አዝማች አያና እዝጊ የተገነባውን “የአያና እዝጊ ቤተ መንግሥት” ጎብኝተዋል።
ዘጋቢለ፡- ያየህ ፈንቴ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!