ኢትዮጵያ ከዓለም ቱሪዝም ድርጅት ሽልማት ተቀበለች።

87
ባሕር ዳር: መጋቢት 04/2015 ዓ.ም (አሚኮ) UNWTO በጎጃም የሚገኘውን የጮቄ ተራራ ኢኮ ቱሪዝም ልማት የዓለም ድንቅ ቱሪዝም መንደር ውድድር አሸናፊ አድርጎ መርጧል::
ሽልማቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ስለሺ ግርማ ከጮቄ ሙሉ ኢኮ ሎጅ ተወካዮች ጋር በመሆን በሳውዲ አረቢያ አሉላ ከተማ ከUNWTO ሴክሬታሪ ጀኔራል ተቀብለዋል።
May be an image of 4 people, people standing and indoor
የUNWTO ሴክሬታሪ ጀኔራል በውድድሩ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ50 ሀገራት በላይ እና ከ100 በላይ የቱሪዝም መዳረሻዎች የተሳተፉ ሲሆን ማኅበረሰቡን ያሳተፉ እና ዘላቂ የሆኑትን ሸልመናል ብለዋል።
በዚህ ደማቅና አኩሪ መርኃ ግብር ላይ በሳውዲ ሀገር የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ መገኘታቸውም ታውቋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“በንግግር ብቻ የሚፈታ ችግር የለም፣ ችግር የሚፈታው በተግባር ነው” በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ስዩም መኮንን
Next articleየአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የማዕከላዊ ኮሚቴ በባሕርዳር ከተማ ባደረገው አስቸኳይ ጉባዔ ከድርጅታዊ ሪፎርምና የጠቅላላ ጉባዔ ዝግጅት ጋር የተያያዙ ውሳኔዎችን አሳለፈ።