
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 02/2015 ዓ.ም (አሚኮ) “ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል ልማት ለዘላቂ የሥራ እድል ፈጠራ” የመድረኩ መሪ መልእክት ነው።
መድረኩ እንደ ሀገርም ኾነ እንደ ክልል ለዘላቂ የሥራ እድል ፈጠራ ሥራው ማነቆ የኾኑ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩና መፍትሔ አመላካች ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ ተብሏል።
በተላይም የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ ትብብራዊ ቅንጅት ለክኅሎት ልማትና ዘላቂ የሥራ እድል ፈጠራ ላይ ሃሳቦች ተነስተው ውይይት እንደሚደረግባቸው ነው ከመርሃግብሩ ለመረዳት የተቻለው።
በምክክር መድረኩ የፌደራል፣ የክልልና የዞን የሥራ ኀላፊዎች፣ ተጋባዥ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች ይሳተፉበታል ተብሏል።
አሚኮ ኦንላይን ጉዳዩን ተከታትሎ መረጃውን ያደርሳል።
ዘጋቢ፦ ጋሻው አደመ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!