የአሚኮ ኦንላይን ሚዲያ መጋቢት 01/2015 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች፦

56

✍️”የአማራ ክልል አሁን ላይ የተረጋጋ ነው” ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር)
✍️በአማራ ክልል ለመልሶ መቋቋም ሥራ 1 ቢሊዮን ብር ተመድቦ እየተሠራ መኾኑን ርእሰ መሥተዳደር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ገለጹ።
✍️አርሶ አደሮች የካሳ ክፍያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙበት የሚያደርግ ተቋም ለማዋቀር እየተሠራ መኾኑን ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ተናገሩ።
✍️በሕግና ሥርዓት ያልተመራ የገበያ ሥርዓት በመኖሩ የዋጋ ንረቱ ከፍ ማለቱን ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ(ዶ.ር) ተናገሩ።
✍️ለቀናት ሲካሄድ የቆዬው የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ ተጠናቀቀ።
✍️ባለፉት ስድስት ወራት በግብርናው ዘርፍ አበረታች ለውጦች መታየታቸውን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
✍️”ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሠላምና ደኅንነትን ለማረጋገጥ በጋራ ለመሥራት ቁርጠኛ ነው” ሃና ቴቴህ
✍️”የኢትዮጵያ ምርቶች በቻይና ገበያ ተደራሽነታቸውን ለማስፋት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ” በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ
✍️”የፖለቲካ ፓርቲዎች በሽግግር ፍትሕ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆን አለባቸው” የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
✍️”በአማራ ክልል 16 ሚሊዮን የሚሆነውን ሕዝብ በጤና መድኅን ማሳተፍ ተችሏል” የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ መልካሙ አብቴ (ዶ.ር)
✍️”የዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ መሆን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት ያስችላል” ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
✍️የባሕር ዳር ከተማን የውኃ አቅርቦት ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት እየሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ውኃ እና ኢነርጅ ቢሮ አስታወቀ።
✍️”ዘመኑ የዲጅታል ነው እና ዘመናዊ ከተማ ለመገንባት አሠራሮቻችን ሁሉ ዘመኑን የዋጁ ማድረግ ያስፈልጋል” ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር)
✍️”የስማርት ሲቲ ትግበራን ዕውን ለማድረግ የነቃ አመራርና ስልጡን ማኅበረሰብ መፍጠርን ይጠይቃል” ረዳት ፕሮፌሰር ዳንኤል ዴኔሮ
✍️14 የፈረስ ጉልበት ያለውና በቀን ከአንድ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚያርስ ተስፋ የተጣለበት የእርሻ መሣሪያ በሀገር ውስጥ ምርት አሻሽሎ ማቅረቡን የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቀ፡፡
✍️የሰዴ ሙጃ እና የስማዳ ወረዳ ነዋሪዎች በራሳቸው አቅም እየሠሩት ላለው መንገድ መንግሥት ድልድይ እንዲገነባላቸው ጠየቁ፡፡
✍️በበለስ-ደብረማርቆስ- ሱሉልታ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ጉዳት ደረሰ።
✍️ኮሪያን ፋውንዴሽን ፎር ኢንተርናሽናል ኼልዝ ኬር በጦርነት የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሶስትዮሽ የስምምነት ውል ተፈራረመ።
✍️ከበጋ መስኖ ስንዴ 70 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ማቀዱን የሰሜን ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ።
✍️”የበልግ ዝናብን በተገቢው መልኩ በመጠቀም የግብርና እንቅስቃሴን ማፋጠን ይገባል” የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየባሕር ዳር ከተማን የውኃ አቅርቦት ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት እየሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ውኃ እና ኢነርጅ ቢሮ አስታወቀ።
Next article“ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሠላምና ደኅንነትን ለማረጋገጥ በጋራ ለመሥራት ቁርጠኛ ነው” ሃና ቴቴህ