ጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ደረጃውን የጠበቀ ነጭ ስኳር ማምረት ጀመረ፡፡

267
ባሕር ዳር:የካቲት 30/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ፋብሪካው ትላንት የካቲት 29/2015 ዓ.ም ነጭ ስኳር ማምረት መጀመሩን አስታውቋል፡፡
በቀጣይም ፋብሪካው ወደ ላቀ የምርት ሂደት ውስጥ በመግባት የታለመውን ግብ ያሳካ ዘንድ ተገቢውን አመራር ለመሥጠት ዝግጁ መሆናቸውን የፋብሪካው የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ሰማ ጥሩነህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡
ለዚህ ስኬት መድረስ እልህ አስጨራሽና ብዙ ውጣ ውረድ ላለፉ አካላት በተለይም ለመላው የድርጅቱ ሠራተኞች ፣ ለማኔጅመንት አባላት እንዲሁም ለጃዊና አካባቢው ኀብረተሰብ በጣና በለስ ሥራ አመራር ቦርድ ስም ምስጋና አቅርበዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleMaxxansa Gaazexaa Hirkoo, Guraandhala 30/2015
Next articleበኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር የሁለተኛ ዙር የሴፍቲኔት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ።