ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፈረንሳይና ጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ

104

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአውሮፓ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካትሪን ኮሎንና እና ከጀርመን የፌደራል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ባየርቦክ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰፈሩት ፥ ጥልቅ እና ፍሬያማ ውይይታችን ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ እና ከጀርመን ጋር ያላትን ጠንካራ እና የቆየ ግንኙነትን የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት እያከናወነች ያለችውን ዘርፈ ብዙ ማሻሻያ፣ ቁልፍ ውጤቶችንና ተያያዥ ችግሮችን አካፍለዋል።

ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ እና ከጀርመን ጋር ያላት ግንኙነት ለበርካታ ዐሠርት ዓመታት መቆየቱንም ነው ያነሱት።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለው ፥ ባለፉት አራት ዓመታት ከሁለቱም ሀገራት ለተደረገው ያልተቋረጠ ድጋፍ አመስግነዋል።

ሁለቱ ሚኒስትሮችም ለውጡን ለማስቀጠል የሚያደርጉትን እገዛ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ማረጋገጣቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Previous article“የሌሎች እምነት እና አስተምህሮን በማንኳሰስ የሚቀርቡ ስብከቶች ሊታረሙ ይገባል” የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ
Next articleፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ከፈረንሳይና ከጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ