6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ የጋራ ልዩ ስብሰባ ዛሬ ይካሔዳል፡፡

96

ባሕር ዳር: ጥር 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ምክር ቤቶቹ በሚያካሂዱት ልዩ ስብሰባ የ2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ የጋራ የመክፈቻ ስብሰባ ቃለጉባዔን መርምሮ በማጽደቅ እንደሚጀመር ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በንብረት ላይ የሚጣለውን ታክስ የባለቤትነት ጥያቄ አስመልክቶ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እና በፌደሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ተጠቁሟል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleብሔራዊ የጸር ሙስና አስተባባሪ ኮሚቴ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት ሥራዎችን ገመገመ።
Next articleበዓለም ከተማ ነዋሪዎች ላይ ቅሬታ የፈጠረው የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት