
አዲስ አበባ፡ ታኅሣሥ 13/2015 ዓ.ም በተመሳሳይ በአዲስ አበባ ከ5 ዓመት በታች ለኾኑ ለ520 ሺህ ህጻናት የተቀናጀ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት በዘመቻ እንደሚሰጥ የአዲስ አበበ ጤና ቢሮ አስታውቋል።
ሀገር አቀፍ የተቀናጀ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ ሥነ- ሥርዓት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሰርጢ ጤና ጣቢያ እየተካሄደ ነው ።
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደረጃ ከ63 ሺህ በላይ ሕጻናት በዘመቻ እንደሚከተቡ ተገልጿል። ክትባቱ በአዲስ አበባ ደረጃ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ይሰጣል ተብሏል ።
በኢትዮጵያ 14 የክትባት አይነት ይሰጣል። ከዚህ ውስጥ የኩፍኝ ክትባት ዋና መኾኑን የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ•ር ደረጄ ዱጉማ ገልጸዋል።
በቀጣይ ሦስት እና አራት አመታት ተፈላጊውን ውጤት እስከሚመጣ ዘመቻ ይቀጥል ብለዋል ሚኒሲቴር ዴኤታው።
ዘጋቢ፡- ዳንኤል መላኩ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!