የተሻሻሉ የጥራጥሬ ሰብልን በማዕከላዊና በሰሜን ጎንደር ዞኖች ለአርሶ አደሮች ምርጥ ዘር በማቅረብ ምርትን ለማሳደግ እየሠራ መኾኑን የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል አስታወቀ ።

126

ጎንደር፡ ሕዳር 29/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ምርምር ማዕከሉ በሽታን የሚቋቋሙ ፣ ከአካባቢ አየር ንብረት ጋር ተስማሚ የኾኑና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የሽንብራ፣ የምስርና፣ የባቄላ ሰብልን

ከ68 ሄክታር በላይ መሬት አርሶ አደሮች እንዲያለሙ እየሠራ መኾኑን የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ምንተስኖት ወርቁ ተናግረዋል ።

 

በዳባትና በወገራ ወረዳዎች ምርታቸው እየቀነሰ የመጣውን የሽንብራና የምስር ሰብልን በተሻሻሉ ዝርያ ባላቸው ዘሮች በመተካት እንዲለሙ እየተደረገ መኾኑንም ኀላፊው ተናግረዋል ።

 

የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል ከአዝዕርትና ከጥራጥሬ ሰብል በተጨማሪ የእንስሳትን ዝርያ ለማሻሻል እየሠራ እንደሚገኝ ገልጿል።

 

ዘጋቢ:- ጳውሎስ አየለ

 

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

 

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq

በዌብሳይት amharaweb.com

በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ

ትዊተር https://bit.ly/336LQaS

ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J

ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO

አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport

አሚኮ መረጃ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck

Previous articleየአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የግብርና ሜካናይዜሽንን ሊያሳድጉ የሚችሉ የተለያዩ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን ተረከበ።
Next articleየአለውሃ ወንዝ የብረት ድልድይ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ገለጸ።