አቶ ደመቀ መኮንን እና የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር በጣና ፎረም ላይ ለመሳተፍ ባሕር ዳር ገቡ

242

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 04/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዛ አብዲ ባሬ በ10ኛው የጣና ፎረም ላይ ለመሳተፍ በዛሬው ዕለት ባሕር ዳር መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

10ኛው የጣና ከዛሬ ጥቅምት 4 እስከ 6 ቀን 2015 ዓ.ም በባሕር ዳር የሚካሄድ መሆኑ ይታወቃል።

ለሀገር ክብር በትግል እናብር‼

Previous articleኢትዮጵያዊነት ብዝኃነት፣ በነፃነት እንደተፈጠሩ በነፃነት መኖር፤ ለእሱም በኅብረት ዋጋ መክፈል እንደኾነ ርእሰ መስተዳድር ሀጅ አወል አርባ ተናገሩ፡፡
Next article❝ሁላችንም አንድ ኾነን የአፍሪካ አህጉርን የሚፈታተኑ ችግሮች ላይ መወያየትና መፍታት ተገቢ ነው❞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)