“በአዲሱ ዓመት ለሀገራችሁ እያደረጋችሁ ያላችሁትን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እጠይቃለሁ” አምባሳደር ስለሺ በቀለ

144

ባሕር ዳር፡ ጳጉሜን 05/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በመላው አሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በአዲሱ ዓመት ለሀገራቸው እያደረጉት ያለውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አምባሳደር ስለሺ በቀለ ጠየቁ።

በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ስለሺ በቀለ፤ በመላው አሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የ2015 ዓ.ም አዲስ ዓመትን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አምባሳደሩ በመልካም ምኞት መልዕክታቸው “በመላው አሜሪካ የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ እንኳን ለ2015 ዓ.ም አዲስ ዓመት አደረሳችሁ” ብለዋል፡፡

“ዓመቱ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆን ልባዊ ምኞቴን እየገለጽኩ ለአገራችሁ እያደረጋችሁ ያላችሁትን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ከአደራ ጭምር እጠይቃለሁ” ብለዋል፡፡

ለሀገር ክብር በትግል እናብር‼

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J

Previous article“የኢትዮጵያን ጠላቶች አንድ ኾነን እንመክታለን፤ አዲሱን ዓመት በፍቅርና በተስፋ እንቀበላለን” የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው
Next article“የኢትዮጵያ አየር ኃይል የጥንካሬ ምንጭ አንድነት ነው፤ አንድነታችንን ይበልጥ በማጠናከር የትኛውንም አይነት ጥቃት በብቃት ለመመከት ዝግጁ ነን” ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ