የንጉሥ ሚካኤል ቤተመንግሥትን በጨረፍታ።

243

👉ንጉሥ ሚካኤል ቤተመንግሥታቸውን ከተንታ ወደ ደሴ በማዛወር ጀሜ በተባለው ከፍተኛ ስፍራ ላይ መሰረቱ።
ይህ ሥፍራ ከጄሜ ኮረብታ እስከ 60 ኪሎ ሜትር እርቀት ለመቆጣጠር የሚያስችል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ቦታ ነው።

👉ከመሀል ሀገር ምፅዋ እንዲሁም ከምእራብ የሀገራችን ክፍል ወደ ታጁራ የሚያልፍን የንግድ መስመር ለመቆጣጠር የነበራቸው ፍላጎት ይህን ሥፍራ ለመቀመጫነት እንዲመርጡት ምክንያት ነበር፡፡

👉አካባቢው ውኃ እና የማገዶ እንጨት በበቂ ሁኔታ መኖሩ አካባቢው እንዲመረጥ አድርጓታል።

👉ቤተመንግሥቱ ከ10 ያላነሱ ክፍሎች ያሉት ዘመናዊ ሕንፃ ነው፡፡

👉ከቤተመንግሥቱ ቅጥር ግቢ የተለያዩ የግብር ሕንፃዎች ይገኛሉ።

👉ከነዚህም ውስጥ የንጉሡ ጽሕፈት ቤት፣ የልጅ እያሱ እልፍኝ፣ የፀሎተ ቤት፣ የችሎት ቤት፣ ግዚያዊ እስርቤት እና ፈትል ቤት ይገኙበታል፡፡

👉ዘግይቶ የተሠራው አይጠየፍ አዳራሽም የዚሁ አካል ነው።
የንጉሥ ሚካኤል ቤተመንግሥት የአስተዳደር መዋቅርና አደረጃጀት ስንመለከት እልፍኝ አስከልካይ፣ ሊቀመ ኳስ፣ ፀሐፌ ትእዛዝ፣ አዛዥ፣ ሊጋባ፣ በጅሮንድ እና ባልደራስ ይሰኛሉ፡፡

👉ደሴ ከተማ እንድትመሠረት እና እንድትሰፋ ትልቁን ሚና የተጫወተው ይሄው ታሪካዊ ቤተመንግሥት ነው።

👉የአይጠየፍ አዳራሽ ግንባታ በ1906 ዓ.ም ተጀምሮ ሥራው በ1907 ዓ.ም ተጠናቋል፡፡

👉ሕንፃው በ2ሺህ 131 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲኾን 45 ሜትር በ27 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡

👉በ10 ሜትር ቁመት በ70 ምሰሶዎች የተዋቀረ የግብር አዳራሽም ነው።
የግብር አዳራሹ ከ5 ሺህ ሰው በላይ ማስተናገድ የሚችልም ነው፡፡

👉ወደ ደሴ ጎራ ብለው ይህን ድንቅ ሥፍራ ይጎብኙ፡፡

አሚኮ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን‼

Previous article“ሀገራዊ የምክክር መድረክ ስኬታማ እንዲኾን በጥንቃቄና በከፍተኛ ኀላፊነት እየተሠራ ነው” ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Next article“ዩኒቨርሲቲዎች የንድፈሃሳብ ልህቀት ብቻ ሳይኾን የተግባር ልህቀትም ማምጣት ይጠበቅባችኋል” የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ