ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በኑሮ ውድነት እና በትምህርት ጉዳዮች የሰጧቸው ማብራሪያዎች፦

159

👉 በባለፉት ሦስት ዓመታት 2 ሺህ 150 ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል፡፡
👉 የተገነቡት ትምህርት ቤቶች ከመዋእለ ሕፃናት ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ደረጃ የሚያካትት ነው።
👉 ከ15 ሺህ በላይ የማስፋፊያ ግንባታዎች በመከናወናቸው ተማሪዎች ሳይጣበቡ እንዲማሩ አስችሏል፡፡
👉 በትምህርት ቤት ምገባ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ተማሪዎች በነጻ ምግብ ያገኛሉ፡፡
👉የኑሮ ውድነትን በተመለከተ፦
👉 ባለፉት ስድስት ወራ መንግሥት 30 ቢሊዮን ብር በመመደብ የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ሠርቷል ነው ያሉት፡፡
👉 ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ መንግሥት ከሕዝብ ትራስፖርት ውጭ የነዳጅ ድጎማን እንደሚያነሳም ነው የተናገሩት፡፡
👉 በኢትዮጵያ የመብራት፣ የውኃ፣ የነዳጅ እና ሌሎች ድጎማዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡
👉የምርት እጥረትና የፍላጎት መጨመር፣ የንግድ ሥርዓቱ መዛባት፣ ምርት እያለ ማቅረብ አለመቻል፣ ግጭትና የገንዘብ አጠቃቀም ጉድለት ለኑሮ ውድነቱ ዋና ምክንያት እንደኾኑም አብራርተዋል፡፡
👉 በዓለም ደረጃ ያለውን የዋጋ ንረት መገንዘብ ተገቢ ነው፤ በበርካታ ሀገራት ከፍተኛ የዋጋ ንረት እንዳለም ጠቁመዋል፡፡
👉 በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ንረት 33 በመቶ መኾኑን አስረድተዋል፡፡
👉 የኑሮ ውድነቱ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ለሚያገኙ ዜጎች አስቸጋሪ መኾኑን አንስተዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ቡሩክ ተሾመ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን‼
ከእኛ ጋር ስለኾኑ እናመሰግናለን‼
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/

Previous articleበኢትዮጵያ አየር መንገድና በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ገለጹ፡፡
Next articleሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች እንደ ሀገር ለማሳካት የተያዘው ዕቅድ በታሰበለት ልክ እንዳይሄድ ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ተናገሩ፡፡