
👉የኢትዮጵያ የደኅንነትና የጸጥታ ተቋማት የጀመሩትን ተቋማዊ ግንባታ አጠናክረው እንዲቀጥሉ፡፡
👉የመንግሥት በሀገሪቱ ሕግ የማስበር ዘመቻ መልካም ውጤቶች እየጠመዘገቡ ነው፡፡ የሕግ ማስበሩ ዘመቻ የኅበረሰቡን የሕግ ይከበርልን ጥያቄ እየመለሰ ስለሆነ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡
👉በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች እየተወሰዱ ያሉ የሕግ ማስከበር እርምጃዎች ተገቢውን የሕግ ስርዓት ያልተከተሉ መሆናቸውን ሕዝቡ እየገለጸ ነው፡፡
👉በሕግ ማስከበሩ እርምጃ በተፈጠሩ ግጭቶች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ ንብረት ውድመት፣ እስራትና እገታ ተፈጽሟል፡፡
👉 ጥፋተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋል ካለባቸው በሕገ መንግሥቱና በፍትሕ ሥርዓቱ መሠረት ብቻ መሆን አለበት፡፡
👉በሕግ ማስከበሩ ሂደት ንጹሐን በጀምላ እንዳይጎዱና እያንዳንዱ እርምጃ በማስረጃ መመስረቱን ለማረጋገጥና የተፈጠሩ ችግሮች ካሉ ማብራሪያ ይሰጥ፡፡
👉ሀገር ለማፍረስ የተነሳውን የሽብር ቡድን ከሌሎች የጸጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን የመከተውን አሁንም በምሽግ የሚገኘውን ፋኖንና የፋኖ አባላትን ማፈንና ማሳደድ አለ የሚል ቅሬታ ስላለ ማብራሪያ ቢሰጥ፡፡
👉ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት የጋዜጠኝነት ነጻነት ግድ ይላል፣ በዚህ ወቅት ግን ጋዜጠኞች እየታሠሩ ነው፣ ጋዜጠኞች ሃሳባቸውን በነጻነት ስለገለፁ ብቻ የሚታሠሩ ከሆነ ከለውጥ በፊት ወደነበረው አፋኝ ስርዓት አይመልስም ወይ፡፡
👉በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀው የሕዳሴ ግድብ አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ነው ያለው፡፡
👉የሌሎች ፕሮጄክቶችስ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በመንግሥት በኩል የተቀመጡ አቅጣጫዎች ምን ይመስላሉ፡፡
👉የኢትዮጵያ ሕዝብ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በብሔር የተጋመደ ነው፡፡ እሴቶቻችን አብረን እንድንኖር መሠረት የኾኑን ናቸው፡፡ ነገር ግን አሁን አሁን በሃይማኖት ሽፋን የሰው ሕይወት ጠፍቷል፣ የሃይማኖት ተቋማት ተቃጥለዋል፣ ሕዝቡም በዚህ ድርጊት እየተማረረ ነው፡፡
👉የጽንፈኝነት ችግር ሀገርን እንደ ሀገር ያጸኑ እሴቶችን በመጉዳት የሀገራችንን ሕዝቦች ለከፋ ጉዳት እየዳረገ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነታችንን በማዳከም ለውጭ ጠላት ተጋላጭ እንድንኾን ያደርገናል፡፡
👉የጽንፈኝነት ችግር በሂደት ሀገራችንን የሚያሳጣ በመኾኑ ችግሩን ለመቅረፍና የጽንፈኝነትን አካሄድ ለመመለስ የመንግሥት አቅጣጫ ምንድን ነው?
👉 በአሸባሪው ቡድን አሁንም የዋግኸምራ፣ ሰሜን ወሎ፣ ሰሜን ጎንደር፣ የአፋር ሕዝብ አሁንም ሰላም አላገኘም፣ ከቀያቸው ተፈናቅለዋል፣ ቀጣናውን ሰላም በማድረግ ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ፣ የሰበዓዊ ድጋፍ እንዲያገኙ ዕቅድ ካለ ቢብራራ?
👉ከትግራይ ክልል እየተፈናቀሉ ወደ አማራ ክልል ለሚገቡ ዜጎችስ የታሰበው ምንድን ነው?
👉የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር መንግሥት ምን እየሠራ ነው? የዘይት የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ማስተካከያ አድርገናል ቢባልም አሁንም እየጨመረ ነው፤ የማስፈጸም ችግር አለ ለምን አይስተካከልም?
👉ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት እርምጃ ተወስዷል ቢባልም የኑሮ ውድነቱ ተባብሷል፡፡ መንግሥት ምን እየሠራ ነው?
👉ጽንፈኛ የማኅበራዊ ሚዲያ አቀንቃኞችን መንግሥት ለመቆጣጠር ምን አስቧል?
በታርቆ ክንዴ
#ኢትዮጵያን እናልማ፣እንገንባ፣እንዘጋጅ ‼️
#ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
#የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
#ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/