400 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ አገራቸው ተመለሱ፡፡

117

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሳዑዲ ዓረቢያ መንግስት ጋር በዳረገው ስምምነት መሠረት ነው በእስር ላይ የነበሩ 400 ኢትዮጵያዊያን ዛሬ ጥቅምት 5/2012 ዓ.ም ወደ ሀገራቸው የተመለሱት፡፡

ኢትዮጵያውያኑ ቀይ ባህርን አቋርጠዉ ሲጓዙ በሳዑዲ ዓረቢያ የጸጥታ ሀይል ተይዘው በእስር ላይ የቆዩ ናቸው ተብሏል።

የዛሬዎቹን ተመላሾች ጨምሮ በበጀት ዓመቱ ባለፉት 3 ወራት ውስጥ 32 ሺህ 890 ኢትዮጵያውያን ከተለያዩ ሀገራት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ብሏል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡

ምንጭ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት

Previous articleተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፀደቀውን የፖለቲካ ፓርቲዎችና የምርጫ አዋጅ ከ90 በላይ የሚሆነውን አንቀጽ በርሃብ የሚቃወሙ መሆኑን አስታወቁ።
Next articleየአማራ ክልል ደኅንነትና የጸጥታ ካውንስል የጋራ መግለጫና ውሳኔዎች