
መጋቢት 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የዘንድሮ የዒድ በዓል ኢትዮጵያ ለእስልምና ሃይማኖት ባለውለታ መሆኗን ለዓለም ዳግም በሚረጋገጥበት መልኩ እንደሚከበር የመርኃግብሩ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ አስታወቁ።
ኡስታዝ አቡበከር ለኢፕድ በሰጡት አስተያየት፣ የዒድ በዓል ትልቁ ምስጢር ከሃይማኖታዊ ኹነት በዘለለ መልኩ አብሮነት፣ ፍቅር፣ መተጋገዝና መተሳሰብ የሚከበርበት በዓል ነው።
ቀደም ሲል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገር ጉዳይ ላይ በውስጥም ኾነ በውጭም ያሉ ኢትዮጵያውያን አጋርነታቸውን በይበልጥ እንዲያጠናክሩ “ዓመት እስከ ዓመት” በሚል መርኃግብር ለዳያስፖራው ማኅበረሰብ ጥሪ እንዳደረጉት ኹሉ ይህንን ታላቅ ጥሪ በመጠቀም “ከዒድ እስከ ዒድ” በሚል ስያሜ ኢትዮጵያ ለእስልምና ሃይማኖት ባለውለታ መሆኗ ለዓለም ዳግም በሚረጋገጥበት መልኩ በልዩ ሁኔታ ይከበራል ነው ያሉት።
#ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
#ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
#የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
#ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/