የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር መጋቢት 4 እንደሚፈጸም ቤተክርስቲያኗ አስታወቀች።

300

የካቲት 29/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር የፊታችን እሁድ መጋቢት 4/2014 ዓ.ም እንደሚፈጸም ቤተክርስቲያኗ አስታወቀች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ተከትሎ ሥርዓተ ቀብራቸውን ለማስፈፅም ቤተክርስቲያኗ የተለያዩ ኮሚቴዎችን አቋቁማለች።

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሥርዓተ ቀብር መርኃግብሩ ቅዳሜ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በመስቀል አደባባይ ሽኝት በማድረግ ይጀመራል።

ከሰንብት በኋላ ወደ በመንበረ ፓትሪያሪክ የጸሎትና ሌሎች ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቶች እንደሚካሄዱ ገልጸዋል።

መጋቢት አራት በሚካሄደው ሥርዓተ ቀብር ሊቃነ ጳጳሳት፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የሃይማኖቱ ተከታዮች እና ሌሎችም በተገኙበት በመንበረ ፓትሪያሪክ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀብር በክብር ይፈጸማል ሲሉ ገልጸዋል።

ዘጋቢ:- አንዱዓለም መናን

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J

Previous articleጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ ሻምበል መማር ጌትነት የክስ መዝገብ ጥፋተኛ በተባሉ ተከሳሾች ላይ የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ፡፡
Next articleፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በኅልውና ዘመቻው ከፍተኛ ተጋድሎ ላደረጉ ሴት የሠራዊት አባላት እውቅና ሰጡ።