የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንትና የተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊ በሽብር ቡድኑ ጉዳት የደረሰባቸውን ሕጻናት ጠየቁ።

118

የካቲት 02/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሐፊ አሚና መሐመድ በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ጉዳት ደርሶባቸው በዱብቲ ሆስፒታል የህክምና ዕርዳታ የሚደረግላቸውን ሕጻናትን ጠየቁ።

ሕጻናቱ ጉዳት የደረሰባቸው የሽብር ቡድኑ በተኮሰው ከባድ መሳሪያ መኾኑ ተገልጿል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንትና የተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊ በተጨማሪም በሠመራ ከተማ የሚገኘውን የዓለም ምግብ ድርጅት መጠባበቂያ መጋዘንን የምግብ ክምችት ተመልክተዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፋር ክልል ርእሰ መሥተዳድር አወል አርባ፣ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።

#ኢትዮጵያን እናልማ፣እንገንባ፣እንዘጋጅ ‼️
#ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
#የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
#ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J

በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በዋግኽምራና በወሎ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/

Previous articleʺየጠላት ግልገል ቁሞ ሲያንቀራጭ፣ በአፉ አስገባበት እንደ አንቃር ቆራጭ “
Next articleኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሳይንስ እና ትምህርት ዘርፍ የሁለትዮሽ ትብብርን ማጠናከር በሚችሉበት ጉዳይ ዙሪያ መከሩ።