በአማራ ክልል ለሚገኙ የፌዴራል ግብር ከፋዮች ዕውቅና እየተሰጠ ነው፡፡

169

ባሕር ዳር፡ መስከረም 24/2012 ዓ/ም (አብመድ) የፌዴራል የገቢዎች ሚኒስቴር የባሕር ዳር ቅርንጫፍ በአማራ ክልል ለሚገኙ 5 ግብር ከፋዮች ዕውቅና እየሰጠ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ደመመ ዕውቅናው ሌሎች በክልሉ የሚገኙ ነጋዴዎችንና ሠራተኞችን የሚያበረታታ መሆኑን ተናረዋል፡፡

ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ በሚያዘጋጀው መድረክ ‹‹በክልሉ የሚገኙ ግብር ከፋዮች እና ሠራተኞች ይመሠገኑበታል፤ ነጋዴዎች ግብር በመክፈላቸው እንዲኮሩ እና ለሌሎች ነጋዴዎች አርአያ እንዲሆኑ ያሰችላል›› ብለዋል፡፡

የዕውቅና መድረኩ አሁን በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ዝርዝር መረጃዎችን የምናደርስ ይሆናል፡፡

ዘጋቢ፡- ብሩክ ተሾመ

Previous articleየሙዚቃ ባለሙያው ኤልያስ መልካ አረፈ፡፡
Next article‹‹የአማራን ሕዝብ ለጥፋት የሚፈልጉ ኃይሎችን በአንድነት፣ ክፍተት ሳይፈጥር፣ የፖለቲካ እና የግጭት ነጋዴዎችን ተልኮ ማክሸፍ አለበት፡፡›› አብን