በጃማይካ የራስተፈሪያን ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ የሚደረገውን የውጭ ጣልቃ ገብነት ተቃወሙ።

137

ታኅሣስ 03/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በጃማይካ የራስተፈሪያን ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ የሚደረገውን የውጭ ጣልቃ ገብነት በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።

ኢትዮጵያውያን፣ ራስተፈሪያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በተሳተፉበት በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ሰልፈኞቹ በኪንግስተን የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ድምጻቸውን አሰምተዋል።

የሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያ መንግሥት እያካሄደ ላለው የኅልውና ዘመቻ እንደሚደግፉም አረጋግጠዋል።

የውጭ ኃይሎች በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉትን ያልተገባ ጣልቃገብነት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።

አሜሪካ እና አጋሮቿ የሽብር ቡድኑን በመደገፍ የያዙት አቋም እንዳሳዘናቸው የገለፁት ሰልፈኞቹ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠውን የኢትዮጵያ መንግሥት ላይ እየተደረገ ያለውን ያልተገባ ጫናን አውግዘዋል።

ኢትዮጵያን ከአጉዋ በማስወጣት አሜሪካ የወሰደችው እርምጃ ተቃውመዋል። የአሜሪካ መንግሥት የያዘው የተዛባ አቋሙን እንዲያስተካክል ጠይቀዋል።

የግዛት አንድነትን የሚፈታተኑ የውጭ ጣልቃገብነቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጥሪ ማቅረባቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation

Previous article“ዘመን ባስ” ወደ ቀያቸው መመለስ ለሚፈልጉ የተፈናቀሉ ወገኖች ለ10 ቀናት የሚቆይ ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ
Next articleየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአማራ ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች 4 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የምግብና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ