“የ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት ይገባል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር)

165
ባሕር ዳር፡ ሕዳር 29/2014 ዓ.ም (አሚኮ) “የ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እና ተሰሚነት እንዲኖራት ሌሎች አፍሪካውያን መሪዎች እያደረጉት ያለውን ንቅናቄ መቀላቀላቸውን አሳውቀዋል።
የአህጉሪቱ ተወካይ በሌለበት አህጉሪቱን የሚመለከቱ ጉዳዮች እና ውሳኔዎች መከናወናቸው ሊቀጥል አይገባም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመልእክታቸው።
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
Previous article❝እየተመዘገበ ያለው ድል በኢትዮጵያ ላይ የሚነሱ ጠላቶች ተሸንፈውና ተዋርደው የሚመለሱ መሆኑን አረጋግጧል❞ አርቲስቶች
Next articleየወገን ጦር የድል ግስጋሴውን እንዲቀጥል ሕዝቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የአማራ ክልል ሚሊሻ ጽሕፈት አቤት ኃላፊ ኮሎኔል ባምላኩ ዓባይ ገለጹ።