ዲያስፖራው የእናት ሀገሩን ጥሪ ተቀብሎ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የሀገሩን እውነት ለዓለም እንዲያሳውቅ ጥሪ ቀረበ፡፡

240
ባሕር ዳር፡ ሕዳር 25/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ባለበት የዓለም ሀገር ሁሉ ስለ ኢትዮጵያ እውነት ንቅናቄ ሲያደርጉ መቆየታቸውን የገለጹት የመንግስት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ይህም በቀላሉ የማይታይ ታላቅ ተጋድሎ ነው ብለዋል፡፡
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ላይ የያዘው የተሳሳተ ግንዛቤ የሚቀረፈው በሁሉም ጥረት እንደሆነ የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ በሚቀጥለው የገና በዓል አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ኢትዮጵያ በመገኘት እውነታውን ለዓለም እንዲያስረዱ ጠይቀዋል፡፡
የንቅናቄውን ሀሳብ ያመነጩት ምስጋና እንደሚገባቸውም አንስተዋል፡፡ “እኛ ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን አናንስም” በሚል የተጀመረው ንቅናቄ ፍሬ እንዲያፈራም የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እቅድ አውጥተው እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን በአሁኑ ወቅት እያደረጉት ያለው የጋራ ጠላትን የማጥፋት ርብርብ በቀጣዩ ተውልድ በታሪክ ሲዘከር እንደሚኖርም በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡
በደጀን አምባቸው
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
Previous articleዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኀን ለፖለቲካ ዓላማ የኢትዮጵያን እውነታ ሲሸፋፍኑ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኀን የሀገራቸውን እውነታ ለዓለም በማስረዳት ኀላፊነታቸውን እንዲወጡ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ጠየቀ፡፡
Next articleየህልውና ዘመቻውን ለመደገፍ ከ3 ቢሊየን 320 ሚሊየን በላይ ገንዘብ መሰብሰቡን የአማራ ክልል የህልውና ዘመቻው አሰባሳቢ ግብረ ኀይል አስታወቀ።