ትውልደ ኢትዮጵያዊው ኦባላ ኦባላ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የፈጸመውን እና እየፈጸመ ያለውን ግፍ ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባይደን ማስረዳቱን ገለጸ፡፡

278
ባሕር ዳር፡ ሕዳር 23/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ትውልደ ኢትዮጵያዊው ኦባላ ኦባላ ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በኢትዮጵያ በቀሰቀሰው ግጭት በርካታ ዜጎችን ለከፋ ችግር መዳረጉን በአገኘው አጋጣሚ አብራርቶላቸዋል።
በጋምቤላ ክልል የተወለደውና በአሜሪካ ሚኔሶታ ኦስቲን የምክር ቤት አባል የሆነው ኦባላ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በመሰረተ ልማት ጉዳዮች ላይ ባተኮረው ስብሰባ ንግግር አድርገው ሲወጡ በአካል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።
በዚህ ወቅትም አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በኢትዮጵያ በቀሰቀሰው ወረራ ምክንያት ኢትዮጵያውያንን ለከፋ ችግርና ስቃይ መዳረጉን ገልጾላቸዋል።
ከፕሬዚዳንት ባይደን ጋር በነበረው ቆይታ በተወለደበት ጋምቤላ ከዚህ ቀደም አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ከተጠነሰሰ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ተርፎ መውጣቱን እንደገለጸላቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መረጃ አስታውቋል።
ከዚህ ባለፈም ሽብርተኛው ትህነግ በሥልጣን ዘመኑ አኝዋኮችን ጨምሮ መላው ኢትዮጵያውያን ላይ ያደረሰባቸውን ሰቆቃ በተመለከተም ማስረዳቱን ይገልጻል። በወቅቱም ፕሬዚዳንቱ የተሰማቸውን ሃዘን እንደገለጹለትም ነው በጽሑፉ ያሰፈረው።
በተጨማሪም በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የግጭት ሴራ እስካሁን ድረስ መላው ኢትዮጵያውያን እያሳለፉትና እየደረሰባቸው ያለውን ግፍ በተመለከተ እና አሜሪካም ይህን ሽብርተኛ ቡድን መደገፍ እንደሌለባት ማብራራቱንም ጠቁሟል።
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
Previous article“አሸባሪው ህውሓት በዚህ ሰዓት እስከ ዛሬ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ ከላይና ከታች እሳት እየነደደበት ነው። ምናልባትም ብዙ መሪዎቹ ሳይሞቱባቸው አይቀርም።
Next articleከኢፌዴሪ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በሳምንታዊ መግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡፡