አይደፈሬው የወገን ጦር በጋሸና ግንባር አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል ይተማመንበት የነበረውን ምሽግ ደርምሶ ጠላትን ድባቅ እየመታ ነው።

587
ባሕር ዳር፡ ሕዳር 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በወገን ጦር የደረሰበትን ከፍተኛ ምት መቋቋም ተስኖት በፈንጂዎች ያጠረውን ኮንክሪት ምሽግ ጥሎ ፈርጥጧል። ጠላት በደረሰበት ድንጋጤ የአባላቱን አስከሬን እንኳን ማንሳት እንዳልቻለ በስፍራው ተገኝተን ተመልክተናል።
የወገን ጦር እየወሰደ ባለው ርምጃ የጠላት መጠቀሚያ የነበሩ የጦር መሳሪያዎች የወደሙ ሲኾን መድፈኛ ታንኮች ከነተተኳሻቸው ተማርከዋል። የማጥቃት ርምጃውን መቋቋም የተሳነው ጠላትም በርካታ ልዩ ልዩ ተተኳሽ ጥይቶችን እያንጠባጠበ ነው የፈረጠጠው።
የአሚኮ የጋዜጠኞች ቡድን በግንባሩ ተገኝቶ እንደተመለከተውም የወገን ጦር በከፍተኛ የጀግንነት ወኔ ጠላትን ድባቅ እየመታው ይገኛል።
ዘጋቢ :- ደጀኔ በቀለ– ከጋሸና ግንባር
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
Previous articleእየተደመሰሰ ያለው ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ቡድን ራሱም ሆነ የዘረፈው ንብረት እንዳይወጣ ሕዝቡ እርምጃ እንዲወስድ ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ጥሪ አቀረቡ።
Next articleየአማራ ሕዝብ የዘረፈውን እና ወገኑን የገደለውን ጠላት እንዲሁ ሊያሳልፈው እንደማይገባ የአማራ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኀላፊ ግዛቸው ሙሉነህ አሳሰቡ፡፡