“በሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኀይል የተከፈተብንን ጦርነት በድል ለማጠናቀቅ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ውስጣዊ አንድነታችን ልናጠናክር ይገባል” የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዱዓለም

178
ፍኖተሰላም፡ ሕዳር 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኀይል ሀገር ለማፍረስ ዓልሞ የከፈተውን ጦርነት በድል ለማጠናቀቅ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ውስጣዊ አንድነትን ማጠናከር እንደሚገባ የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለም ገልጸዋል፡፡
ወቅታዊ የህልውና ዘመቻውን በማስመልከት የፌዴራል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ ሕዝባዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኀይል የፈጸመውን ወረራ መመከት እና ወራሪ ኀይሉ ወረራ ካካሄደባቸው የአማራና አፋር ክልሎች ሳይወጣ ባለበት መቅበር የመላ ኢትዮጵያውያን አሁናዊ ተጋድሎ ነው፡፡ በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያውያን ከፀጥታ ኀይሉ ጋር በመቀናጀት በአኩሪ ድል በሁሉም ግንባሮች ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኀይልን እየቀበሩት ይገኛል፡፡
ይህንን ወቅታዊ አጀንዳ አስመልክቶ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ በተካሄደ ሕዝባዊ ውይይት ሕዝቡ ለሰራዊቱ አስተማማኝ ደጀን ከመሆን ጀምሮ ግንባር እስከ መዝመት የደረሰ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረገ ስለመሆኑ ተነስቷል፡፡
በውይይቱ ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኀይል ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች ዘልቆ በመግባት ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱን በመግለጽ ወጣቱ ትውልድ መከላከያ ሠራዊቱን በመቀላቀል እናት ሀገሩን ከወራሪ ጠላት ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል፡፡
የተጀመረው የህልውና ዘመቻ በድል እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን የተናገሩት አቶ በላይነህ ሀገር ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ እንዲቀጥል ሁሉም በጋራ ሊነሳ ይገባል ብለዋል፡፡
የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መልካሙ ተሾመ የዞኑ ሕዝብ ለህልውና ዘመቻው ሁለንተናዊ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አረጋግጠው አሁንም ወጣቱ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ክልሉ ብሎም ሀገሪቱ አሁን ከገጠማት ችግር የምትወጣው የሀገር መከላከያ ሠራዊትን በማጠናከር በመሆኑ ወጣቶች መከላከያን እንዲቀላቀሉ ሁሉም አካል ሊሠራ ይገባል ያሉት ደግሞ በውይይቱ የተገኙት የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ናቸው፡፡ ግንባር ከመዝመት ባሻገርም ለዘማች ቤተሰብና ለሠራዊቱ የሚደረገው የደጀንነት ተግባር እና አካባቢን በንቃት መጠበቅ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለም “በሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኀይል የተከፈተብንን ጦርነት በድል ለማጠናቀቅ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ውስጣዊ አንድነታችን ልናጠናክር ይገባል” ብለዋል፡፡ የተጀመረውን የህልውና ዘመቻ በድል ለማጠናቀቅ አንድነት፣ አስተማማኝ ደጀንነት እና ሠራዊቱን መቀላቀል የሚሉ ወሳኝ ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅም አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ዘመኑ ይርጋ – ከፍኖተ ሰላም
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
Previous article“በቅርብ ቀን የህልውና ዘመቻውን በድል አጠናቅቀን በጋራ እጅ ለእጅ ተያይዘን የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር በጠላት #መቃብር ላይ ቆመን እንዘምራለን” የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Next articleከጥንት እስከ ዛሬ የድል አብሪ ኮከቦች – ኢትዮጵያውያን