የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች “ተከትለንሃል” በሚል ወደ ጦር ግንባር እየዘመቱ ነው።

133
ሕዳር 18/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና አርቲስቶች “ተከትለንሃል” በሚል ሐሳብ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አህመድ (ዶ.ር) ን በመከተል ወደ ጦር ግንባር እየዘመቱ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የከተማዋ ነዋሪዎች የሀገር ሉዓላዊነትን ለማስከበር ወደ ጦር ግንባር ለሚዘምቱ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና አርቲስቶች አሸኛኘት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
በአሸኛኘት መርኃ ግብሩ ላይ የከተማዋ አስተዳደር አመራሮች፣ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና አርቲስቶች የአሸኛኘት ሥነ ሥርዓት ላይ መገኘታቸውን ኦቢኤን ዘግቧል።
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
Previous articleበአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ከዳያስፖራው ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማሰባሰብ ተችሏል።
Next article“ራሱን ለሀገሩ አሳልፎ ለሰጠው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አብሮ በመዝመት እና በመደገፍ ደጀንነታችንን እናረጋግጣለን” የደባርቅ ከተማ ነጋዴዎች