
ጦርነቱ በከፍተኛ ድል እየተከናወነ መሆኑን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ፡፡
ሕዳር 17/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሠራዊቱ በከፍተኛ ወኔ ጠላትን እየተፋለመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ካሳጊታን መቆጣጠር እንደተቻለና ሠራዊቱ በከፍተኛ ግስጋሴ ላይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ነጻነት እስኪረጋገጥ ወደኋላ አንልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምንፈልገው እኛ ተሰውተን የሚኮሩ ኢትዮጵያውያንን ማየት ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም ሕዝባችን ከጎናችን ነው፤ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንም እየደገፉን ነው፤ ጠላት ከእኛ ጋር ሊፎካከር አይችልም፤ እናሸንፋለን፣ ነጻና ብልጽግናዋ የተረጋገጠች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን እናሸጋግራለን ብለዋል፡፡
#ተነሳ!!
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
#አካባቢህን ጠብቅ!! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
