በእስራኤል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አንዳንድ ምዕራባውያን ሀገራት በኢትዮጵያ ላይ እያደረጉ ያሉትን ጫና በመቃወም ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡

608
ሕዳር 12/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በእስራኤል የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን አንዳንድ ምዕራባውያን ሀገራት በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉት ጫና እንዲያቆሙ እያካሄዱ ባሉት ሰላማዊ ሰልፍ ጠይቀዋል፡፡
እስራኤል ለኢትዮጵያ መንግሥት የምትሰጠውን ድጋፍ አጠናክራ እንድትቀጥልም ሰልፈኞቹ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ መግባት ይቁም ፣ በሐሰት መረጃ የሚነዛው ውዥንብር ይቁም ፣ በኢትዮጵያ ላይ የሚካሄደው የማዕቀብ ዘመቻ ይቁም የሚሉና ሌሎች መልዕክቶች በሰልፉ ላይ እየተላለፉ መሆኑን በእስራኤል የኢትዮጵያ ኤምባሲ የማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleበአሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አደረጉ፡፡
Next article“ጽናት ካለ ድንጋይና መጥረቢያም ቦምብ ነው”