
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 29/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የምንታወቅበትን ወቅት ሳንታወክ ማለፍ የብሔራዊ ጽናት ምልክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ገለፁ።
“በብዙ አቅጣጫዎች እየተፈተንን ነው፤ ፈተናውን የምናልፍበት ጥንካሬያችን የጀመርነውን ጉዞ እውን ለማድረግ ካለን የጋራ ፍላጎት የሚመነጭ ነው” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት “ወደ ኋላ የሚጎትተን ቢበዛም በብርቱ ክንድ፣ በጸና ልቡና፣ ለድል በሚገሰግስ መንፈስ የኢትዮጵያን አሸናፊነት እናበስራለን” ነው ያሉት።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ