አመልድ ደረጃውን የጠበቀ ጋራዥ ከሁለት ወራት በኋላ ወደ ሥራ ሊያስገባ ነው፡፡

500

ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2012 ዓ/ም (አብመድ) የአማራ መልሶ መቋቋምና ልማት ድርጅት (አመልድ) በባሕር ዳር ከተማ ከፍተኛ ጥራት ያለውና በርካታ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ጋራዥ ለማቋቋም እየሠራ ነው፡፡

የአመልድ ዋና ዳይሬክተር ዓለማየሁ ዋሴ (ዶክተር) እንደተናገሩት ድርጅቱ በ20 ሚሊዮን ብር ነው ጋራዡን በባሕር ዳር የሚገነባው፡፡ ጋራዡ ለድርጅቱ የገቢ ማስገኛ ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን የሚገኘው ትርፍም በክልሉ ለሚሠሩ የልማት ሥራዎች ማጠናከሪያ እንደሚውልም ተመላክቷል፡፡

ዳይሬክተሩ እንዳሉትም ጋራዡ የአመልድ፣ የመንግሥት፣ የድርጅቶችና የግል ተሽከርካሪዎችን የመመርመርና የመጠገን አገልግሎት ለመስጠት የሚችል ነው፡፡

ጋራዡ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ወደ ሥራ ለማስገባት አመልድ ጥረት እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ምንጭ፡- አመልድ

Previous article7ተኛው የኢትዮ-ሩስያ የጋራ ኮሚሽን ጉባኤ በሩስያ ፒተርሰበርግ ከተማ እየተካሄደ ነው።
Next articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ልዩ ልዑክን ተቀብለው አነጋገሩ፡፡