7ተኛው የኢትዮ-ሩስያ የጋራ ኮሚሽን ጉባኤ በሩስያ ፒተርሰበርግ ከተማ እየተካሄደ ነው።

204

ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2012 ዓ/ም (አብመድ) 7ተኛው የኢትዮ-ሩስያ የጋራ ኮሚሽን ጉባኤ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊ፣ ቴክኒካዊና የንግድ ትብብር አጀንዳዎች ላይ አተኩሮ በሩሲያ ፒተርስበርግ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

የኢፌዴሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያ (ዶክተር ኢንጂነር) የተመራ የልዑክ በጉባኤው ላይ እየተሳተፈ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡

በጉባኤው የንግድ ትብብር፣ የኢኮኖሚ ትብብር፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአማራጭ የኃይል ምንጮች፣ የህዋ ቴክኖሎጂ፣ የዲጅታል ቴክኖሎጅ መገናኛ ዘዴዎች፣ የባሕልና ቱሪዝምና ሌሎች አዳዲስ የትብብር ማዕቀፎችና የትኩረት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ዝርዝር ጉዳዮች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የኒውክለር ኃይል አማራጮችን ለሠላማዊ አገልግሎት በስፋት ለመጠቀም የሚያስችል ፕሮቶኮልም አንዱ የመወያያ አጀንዳ እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡

ከጉባኤው ኢትዮጵያ እያካሄደቻቸው ላሉ ሀገራዊ ለውጦች
አጋዥ የሆኑ የትብብር ማዕቀፎችና ስምምነቶች ግብዓት ያገኛሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡

ኢትዮጵያ እና ሩስያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት አላቸው፡፡

Previous articleከሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ልዑካን ጋር ከቤተ ክርስቲያኗ ባሻገር በጤና፣ በትምህርትና ተያያዥ ጉዳዮች በትብብር ለመሥራት ውይይት ተደርጓል።
Next articleአመልድ ደረጃውን የጠበቀ ጋራዥ ከሁለት ወራት በኋላ ወደ ሥራ ሊያስገባ ነው፡፡