የኢትዮጵያ የማራቶን አትሌቶች ለሦስት ወራት ከውድድር ታገዱ፡፡

111

ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2012 ዓ/ም (አብመድ) በ17ኛው የዶሃ ዓለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና ላይ የተካፈሉ የኢትዮጵያ የማራቶን አትሌቶች በሙሉ ለጤንነትና ለአስተዳደራዊ አሠራር ሲባል ከ3 ወር በፊት ምንም ዓይነት ውድድር ማድረግ እንደሌለባቸው በዶሃ የተገኘው የፌዴሬሽኑ አመራር ወሰነ።

አመራሩ ይህንን ውሳኔ የሚመለከታቸው ሁሉ እንዲያከብሩም በጥብቅ አሳስቧል።

ውሳኔውን መተላለፍ ከበድ ያለ እርምጃ እንደሚያስከትልም አስጠንቅቋል።

በዶሃ በተካሄደው የማራቶን ውድድር ሁሉም ኢትዮጵያን የወከሉ ሴት አትሌቶች ውድድሩን በሙቀት ምክንያት ማቋረጣቸው መገለጹ የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

Previous articleኃላፊነት የጎደለው ዕለታዊ እንቅስቃሴ በጣና ሐይቅ ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው፡፡
Next articleየሞሐመድ ፋራህ የቀድሞው አሰልጣኝ ለአራት ዓመታት ዕገዳ ተጣለባቸው፡፡