
ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2012 ዓ/ም (አብመድ) በዓለም ለ29ኛ እና በኢትዮጵያ ለ28ኛ ጊዜ ‹‹የዕድሜ ባለጸጎችን በመደገፍ እንመረቅ!›› በሚል መሪ መልዕክት በአዲስ አበባ ሚሊኒዬም አዳራሽ እየተከበር ይገኛል።
በበዓሉ ላይም ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ፣ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶክተር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢ.ፕ.ድ እንደዘገበው በዓሉ የመረዳዳትና የመደጋገፍ መልካም እሴትን በመተግበር ነው እየተከበረ የሚገኘው፡፡