ኳታር ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር) የደስታ መግለጫ ላከች።

247

ባሕር ዳር፡ መስከረም 28/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኳታሩ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አልታኒ፣ ምክትል አሚር ሼክ አብዱላህ ቢን ሃማድ አል ታኒ እና የኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ ሼክ ካሊድ ቢን ካሊፋ ቢን አብዱላዚዝ አልታኒ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመሾማቸው የደስታ መግለጫ ልከዋል።

መሪዎቹ በላኩት የደስታ መግለጫ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ዶክተር ዐቢይ ለሀገራቸው እና ሕዝባቸው ልማት እና ብልፅግና የተሻለ ስኬት እንዲያስመዘግቡ መልካም ምኞታቸውንም ገልፀዋል። መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ነው

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleተቋማት በሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ አሳሰበ።
Next articleየኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ በለጠ ሞላ ከቀድሞው ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ ጋር የሥራ ርክክብ አድርገዋል።