ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ጋር በሀገራቱ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

235
መስከረም 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ.ር) ከተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
በውይይታቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የወዳጅነትና የትብብር ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ መክረዋል፡፡
መሪዎቹ በጋራ እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያም ውይይት አድርገዋል፡፡
መሐመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በድጋሚ በመመረጣቸውም የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት ማስተላለፋቸውን የኢሚሬት ዜና ወኪል ዘግቧል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article❝አዲስ ተሿሚ ሚኒስትሮች ኢትዮጵያ ያለችበትን አሁናዊ ሁኔታ በመረዳት መፍትሔ ሊሰጡ ይገባል❞ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሶሾሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ
Next articleዜና መጽሔት ባሕር ዳር ፡ መስከረም 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ)