40ኛው ዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ጉባኤ በካናዳ ሞንትሪያል እየተካሄደ ነው፡፡

161

ባሕር ዳር፡ መስከረም 19/2012 ዓ/ም (አብመድ) ዓለም አቀፍ የሲቪል አቬሽን ድርጅት ከተመሠረተ 75ኛ ዓመቱ ነው፤ በጉባኤውም ከመሥራች ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በትራንስፖርት ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ ተወክላ እየተሳተፈች ነው፡፡

ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያበረከተች ላለው አስተዋጽኦ በተለይም በ‹ኢንተርናሽናል ሬቨኑ ፓሴንጀር ሬት› 90 ከመቶ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ 36 የዓለም ሀገራት ውስጥ አንዷና በአፍሪካም በቀዳሚነት ደረጃ የምትገኝ መሆኗ በጉባኤው መነሳቱትን ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ በማኅበራዊ ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

Previous articleየመቀንጨር ስርጭት ቢቀንስም የተጀመረው ሥራ በሚፈለገው ልክ ውጤታማ አለመሆኑ ተገለጸ፡፡
Next articleከ2ሺህ 500 በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች ወደ ግሸን መናኸሪያዎች ገብተዋል፡፡