“ምክር ቤቶቹ የሕዝብ ስሜት የሚንጸባረቅበት፣ የሚስተጋባበት፣ የተለያዩ ሐሳቦች የሚንሸራሸሩበት፣ የሚፋጩበት፣ ተከራክረው የሚያሸንፉበት ቦታ መሆን ይጠበቅባቸዋል” የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ

142
መስከረም 24/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ፌዴሬሽን ምክር ቤት የምስረታ እና መክፈቻ ጉባዔ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ባደረጉት ንግግር ለተመረጡ የምክር ቤት አባላት ለዚህ ከፍተኛ ኀላፊነት ስለመመረጣቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
የተመረጡበት ወቅት ለሀገሪቱ ልዩ በመሆኑ የስኬት የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡ እዚህ ለመድረስ ብዙ ዋጋ መከፈሉን ያነሱት ፕሬዝዳንቷ ለዚህ አዲስ ምዕራፍ መባቻ ላይ ለመድረስ መስዋእትነት የከፈሉ ውድ ኢትዮጵያውን ክብር እንደሚገባቸውም ፕሬዝዳንቷ አንስተዋል፡፡
የምክር ቤቶቹ አባላት የመረጣቸውን ሕዝብ ፍላጎት ማወቅ እና በምክር ቤቶቹ ተመራጮች ቃል የገቡትን እንዲፈጽሙ እንደሚከታተሉ እምነታቸውን አስታውቀዋል፡፡
ፓርላማ የሕዝብን የልብ ትርታ ለማወቅ እድል ያለው ነው፤ በየጊዜው እያደጉ የሚመጡ የሕዝብ ፍላጎቶችን ለማወቅ እድል ይሠጣል ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንቷ “ምክር ቤቶቹ የሕዝብ ስሜት የሚንጸባረቅበት፣ የሚስተጋባበት፣ የተለያዩ ሐሳቦች የሚንሸራሸሩበት፣ የሚፋጩበት፣ ተከራክረው የሚያሸንፉበት ቦታ መሆን ይጠበቅባቸዋል” ነው ያሉት፡፡
ዘጋቢ፡- የማነብርሃን ጌታቸው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ለምክር ቤቱ ያስተላለፉት መልዕክት፡፡
Next articleየኢትዮጵያ መንግሥት ምሥረታ እና ምላሽ የሚሹ የሕዝብ ጥያቄዎች።