የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር መስራች ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።

943
ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ምክር ቤቱ በውሎው የሚከተሉትን መርሃ ግብሮች ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል:-
-የምክር ቤት አባላት ቃለ መሃላ ይፈጽማሉ
-የአፈ-ጉባዔ አስመራጭ ኮሚቴ ምርጫ ይካሄዳል
-የአፈ-ጉባዔ እና የምክትል አፈ-ጉባዔ ምርጫ ይከናወናል
-የአፈ-ጉባዔ እና የምክትል አፈ-ጉባዔ ቃለ-መሃላ ይፈጸማል
-የነባር አፈ-ጉባዔ ከአዲስ አፈ-ጉባዔ ርክክብ ይካሄዳል፣አፈ-ጉባዔ ንግግር ያደርጋሉ
-ቋሚ ኮሚቴዎች ይሰየማሉ
-ቋሚ ኮሚቴዎች ቃለመሃላ ይፈጽማሉ
-የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ይሰይማሉ
-የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ቃለ መሃላ ይፈጽማሉ
-የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ንግግር ያደርጋሉ
-ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የካቢኔ ሹመቶች ቀርበው በምክር ቤቱ ይጸድቃሉ
-ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ቃለ መሃላ ይፈጽማሉ
-በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የተሾሙ ቃለ-መሃላ ይፈጽማሉ
-የካቢኔ አባላት ቃለ-መሃላ ይፈጽማሉ
-የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የዳኞች አስተዳድር ጉባዔ የምክር ቤት ወኪሎች ይሰየማሉ።
ዘጋቢ፦ አዳሙ ሽባባው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ ድሮኖችን ለቀረፃ ሲጠቀምና ሲያበር የተገኘ ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ በሕግ እንደሚጠየቅ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ።
Next article“ሕዝብን ለማገልገል መመረጥ ትልቅ እድል ነው” የአማራ ክልል የምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ