
ጎንደር፡ መስከረም 16/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ከተማ አስተዳደር እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሥራ ኀላፊዎች ለህልውና ዘመቻው የሚሆን ገንዘብ ለማሰባሰብ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የንግድ ተቋማት በመዘዋወር እንኳን አደረሳችሁ እያሉ ነው።
የህልውና ዘመቻውን በሁሉም ዘርፍ ማጠናከርን ዓላማ ያደረገው የሥራ ኀላፊዎቹ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የመስቀልን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክትም የያዘ ነው።
የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ ”እንጎሮጎባሽ” በማለት 3 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብም ታቅዷል፡፡
ዘጋቢ፡-ጳውሎስ አየለ-ጎንደር
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ