በአጣዬ ከተማ አስተዳደር እና አካባቢው ዘላቂ ሰላም መገንባትን ዓላማ ያደረገ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

118
ባሕር ዳር፡ መስከረም 16/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በአጣዬ ከተማና አካባቢው ተከስቶ በነበረው የሰላም እጦት በነዋሪዎች ላይ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች ደርሰዋል።
ከዚህ ችግር ማግስት አካባቢው መልሶ እንዲረጋጋና ዜጎችም እንዲቋቋሙ እየተሠራ ነው።
እየሩሳሌም የሕፃናትና ማኅበረሰብ ልማት ድርጅት ያዘጋጀው ውይይት በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን የመገንባት ዓላማ ይዞ በአጣዬ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አገኘሁ መክቴ አሁን በከተማዋ እየመጣ ያለውን ሰላም ማስቀጠል ይገባናል ብለዋል።
አሸባሪው ትህነግ የፈጸመውን ወረራ አስከፊነት ከኛ በላይ የሚረዳ የለም ያሉት ከንቲባው ወረራውን በአንድነት መክተን ሰላማችንን ማረጋገጥ ይገባናል ብለዋል።
በአካባቢው የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት ተወካይ ኮሎኔል ተከተል ልኬን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የፀጥታ አካላት እና በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች የውይይቱ ተሳታፊ ሆነዋል። ውይይቱ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣም ያግዛል ተብሏል።
ዘጋቢ፡-ኤልያስ ፈጠነ -ከአጣዬ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 76ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር።
Next articleየመስቀል በዓልን አስመልክቶ የጎንደር ከተማ አስተዳደር እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሥራ ኀላፊዎች ለህልውና ዘመቻው የገንዘብ ድጋፍ እያሰባሰቡ ነው፡፡